የቂርቆስ ክፍለ ከተማ
መስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት

የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት

በከተማችንን ብሎም በክ/ከተማችን የሚታየውን ድህነትና ስራ አጥነት ለመቀነስ ለአብዛኛው የሕብረተሰብ ክፍል በተለይም ሴቶችንና ወጣቶችን በጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በማደራጀት የስራ እድል እየተፈጠረላቸዉ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ በተለይ የማምረቻ፣ የመሸጫ እና የማሳያ ቦታ አቅርቦት በሚፈለገው ደረጃ እና ፍጥነት ለኢንተርፕራይዞች ማቅረብ አለመቻሉ እንዲሁም ተሰርተው የቀረቡ የመስሪያ ቦታዎች የሚገነቡባቸው ቦታዎች ምቹ አለመሆን፣ የግንባታ ጥራት መጓደልና መጓተት፤ መሰረተ ልማት ያልተሟላላቸው መሆናቸው ከዘርፉ የሚጠበቀውን ውጤት በሚፈለገው ደረጃ ማድረስ አልተቻለም፡፡

ስለሆነም በክፍለ ከተማው የሚታየውን የማምረቻ፣ማሳያ እና መሸጫ ቦታ ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ መንግስታዊ ተቋማትን በማሳተፍ አስፈላጊውን ስትራቴጂ በመንደፍ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ የመስሪያ ቦታ ልማት እና አስተዳደር ጽ/ቤት የመስሪያ ቦታዎችን በማልማት እና በማስተዳደር በዘርፉ ያለውን የመስሪያ ቦታዎች ልማት እና አስተዳደር ችግሮች...... ተጨማሪ ያንብቡ

ፍጹም ግረፌ ገ/ህይወት , የቂርቆስ መስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ
image description

የጽ/ቤቱ ቡድን መሪዎች

ቤተልሄም ሀብታሙ

የመስሪያ ቦታ ማደራጀት፣ የማስተላለፍና መረጃ ጥንቅር ቡድን መሪ

ለሜሳ ጎበና

የመስሪያ ቦታ ልማት ስራዎች አቅርቦት ቡድን መሪ

አቶ አሸናፊ ካህሳይ

የመስሪያ ቦታ ልማት ስራዎች የደንበኞች አገልግሎት ቅሬታ አበቱታ አፈታት ቡድን መሪ

አቶ አቶ ሌሎ

የመስሪያ ቦታዎች አካባቢ ሚቹነት ደህንነትና ቁጥጥር ቡድን መሪ

የቂርቆስ ክ/ከተማ መስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቂርቆስ ክ/ከተማ የመስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት ከተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መነሻ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የለውጥ ሥራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ በብቃቱና እና በሥነ-ምግባሩ የተመሰገነ የሰው ኃይል እንዲመራ በማድረግ ለተገልጋዮቹ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በአዲስ መልክ በመለየት አደራጅቷል፡፡

በተጨማሪም በጽ/ቤት የሚሰጠው አገልግሎት የተገልጋይ ፍላጎትን ማዕከል አድርጎ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል የሚሰጡ የአገልግሎት አይነቶች፣ አገልግሎቱ የሚሰጥበት ስታንዳርድ፣ የሚሰጥበትን ቦታ እና ከተገልጋይ የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎችን በግልጽ በዝርዝር በማስቀመጥ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሰረት ፍህታዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡና ተገልጋዮች ምን ዓይነት አገልግሎት በምን ዓይነት ደረጃ ማግኘት እንደሚገባቸው ግንዛቤ በመፍጠር በዚህም ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲኖር፣ በህዝብና መንግስት መካከል መተማመን እንዲፈጠር፣ ልማትና ዲሞክራሲ እንዲያብብ ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው፡፡ በመሆኑም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂት ለመፍታት በምናደርገው ጥረት ባለድርሻ አካላትና ህብረተሱቡ ከጽ/ቤቱ ጎን እንዲቆሙ እናሳስባለን፡፡